Back
‘አማራነት’ን መፍራት (Amhara Phobia) – በገ/ክርስቶስ ዓባይ
Jul 29, 2020
በገ/ክርስቶስ ዓባይ ሐምሌ 23 ቀን 2012 ዓ/ም
የአማራነትን ምሥጢር ለመረዳት እጅግ በጣም የመጠቀና የጠለቀ ዕውቀት ያስፈልጋል። ታላቁ መጽሐፍ እንደሚናገረው “የጥበብ መጀመሪያው እግዚአብሔርን መፍራት ነው!” እንግዲህ እግዚአብሔርን የማያውቅ ወይም ደግሞ የማይፈራ ሁሉ የአማራነትን ምስጢር ለመመርመርና ለመረዳት ከቶ አይችልም። ስለሆነም አማራ ያልሆኑ ሁሉ የበታችነት ስሜት ይንጣቸዋል፤ ያሰቃያቸዋል። ከዚህም የተነሣ አማራነትን ይፈራሉ፤ ይንቀጠቀጡማል። በመሠረቱ አማራነት እንዴት ተወለደ (ተፈጠረ)?
የአማርኛ ቋንቋ እስከ 950 ዓ/ም ድረስ በአክሱም ቤት መንግሥት የልዑላዊያን ቤተሰቦች ልዩ የመግባቢያ ቋንቋ ተደርጎ ይወሰድ ነበር። አማርኛን የሚናገሩት በጣም የተማሩ፤ የተመራመሩ፤ ፈጣሪያቸው የሆነውን እግዚአብሔርን እጅግ የሚፈሩና የሚያመልኩ ነበሩ። ነገር ግን የአክሱም ሥርወ መንግሥት የመጨረሻው ንጉሥ የነበረው ‘አንበሳ ውድም’ በጣም የደከመ መንግሥት ከመሆኑ የተነሳ በዮዲት ጉዲት በደረሰበት ድንገተኛ ጥቃት ከሥልጣን ተወግዶ ወደ ደቡብ በመሸሽ (አማራ ሳይንት) አሁን መካነ ሰላም እየተባለ በሚጠራው የወሎ ግዛት አካባቢ መሥፈሩ ይታወቃል።
ከዚያም የአማራነት ሥነ ልቡና በአካባቢው ቀስ በቀስ እየተዛመተ መስፋፋት ጀመረ። አማራነት አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪነት ብቻ እንዳልሆነ ከዚህ ቀጥሎ ለማብራራት እሞክራለሁ። አማራነት ከላይ እንደተጠቆመው በቅድሚያ ‘እግዚአብሔርን መፍራት ነው!’ ቀጥሎም ሠራተኛና በራሱ ላብ የሚተዳደር እንጂ የማንንም ሰው የግል ሀብትና ንብረት በመዝረፍ ለመበልጸግ አይደፍርም። ሁሉን የሚያይ አምላክ አለና! እንዲህ ያለውን ቅሌትና የወረደ ተግባር በምንም መልኩ አይፈጽምም።
አማራነት ሙሉ እምነቱን በፈጣሪው ላይ የጣለ ስለሆነ ማንንም አይፈራም። ከመጠን ያለፈ በራስ መተማመን አለው። በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረውን ማንኛውንም ሰው ያከብራል። ሰውን ያከብራል ስንል፤ ራሱን የበታች አድርጎ እንዳልሆነ መታወቅ አለበት። ከሃይማኖቱ በወረሰው መሠረት ልክ እንደ ጻድቁ አብርሃም  እንግዳ ተቀባይ ነው። የእግዚአብሔር እንግዳ ወደ ቤቱ ከሄደ እግሩን አጥቦ፤ ምግብ አብልቶ፤ መኝታ ጎዝጉዞ በደንብ ያስተናግዳል። ይህ ከአማራነት መገለጫዎች እንደ አንዱ አድርገን ልንወስደው እንችላላን።
እንግዲህ ይህ የአማራነት ሥነ ልቡና በአካባቢው የሚኖሩትንና የተለያየ ቋንቋ ተናጋሪ የነበሩትን ሁሉ በፍቅር እያቸነፈ ማረካቸው። በዚህ ሁኔታ ቋንቋው፤ የሥራ ባህሉ፤ ሃይማኖቱና ሥነ ምግባሩ ሁሉንም አጥለቀለቀ። ከሁሉም በላይ ቋንቋው የግዕዝ ፊደላትንም የተላበሰ በመሆኑና በቀላሉ ለማንበብና ለመጻፍ በማስቻሉ ግዛቱን በኃይል ሳይሆን በፍላጎት እንዳስፋፋ ለመገመት አያስቸግርም።
8Shares
1Comments
0Favorites
9Likes
Say something to impress...
Loading...
Comments
Hot

No content at this moment.

Relevant people
Zehabesha
6663 Followers
Latest Ethiopian News Provider
Related